am_tn/job/36/06.md

1.5 KiB

እርሱ ዐይኖቹን ከጻድቅ ሰው ላይ አያነሳም

ኤሊሁ እግዚአብሔር ለጻድቅ ሰው ሚያደርገውን ጥበቃ የመገልጸው እግዘአብሔር በዐይን እንደሚከታተላቸው አድርጎ ሲሆን እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ የሚያደርገውን ጥበቃ ማቆሙን ደግሞ ዐይኖቹን ከላያቸው ማንሳት አድርጎ ይገልጸዋል፡፡ "እርሱ ጻድቃን ሰዎችን መጠበቁን አያቆምም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እንደ ንጉሥ በዙፋን ላይ ያስቀምጣቸዋል

ኤሊሁ እግዚአብሔር ለጻድቃን የሚሰጠውን ክብር የሚገልጸው እንደ ንጉሥ በዙፋን ላይ እንደሚያስቀምጣቸው አድርጎ ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እነርሱ ከፍ ይላሉ

ኤሊሁ እግዚአብሔር ጻድቃንን የሚያከብራቸው ከፍ ወዳለ ስፍራ እንደሚያወጣቸው አድርጎ ነው፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍት ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "እርሱ ወደ ላይ ከፍ ያደርጋቸዋል" ወይም "እርሱ ያከብራቸዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)