am_tn/job/35/09.md

1.2 KiB

አጠቃላ መረጃ፡

ኤሊሁ ንግግሩን ቀጠለ፡፡

በብዙ የተጽዕኖ ድርጊቶች ምክንያት

"ተጽዕኖ" የሚለው ቃል በግሳዊ ሀረግ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "ሰዎች ሌሎችን ለመጨቆን በሚያደርጓቸው በርካታ ነገሮች ምክንያት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

ከታላላቅ ሰዎች ክንዶች እርዳታን ይፈልጋሉ

እዚህ ስፍራ "ክንዶች" የሚለው የሚያመለክተው ሀይልን ወይም ጥንካሬን ነው፡፡ "ከታላላቅ ሰዎች ሀይል ለማግኘት ጥሪ ያደርጋሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

በምሽት ዝማሬዎችን የሚሰጥ ማን ነው

ኤሊሁ እግዚአብሔር ለሰዎች በችግር ጊዜ፣ በምሽት ሰአት የሚዘምሩት ዝማሬ አድርጎ ተስፋን እንደሚሰጥ ይናገራል፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)