am_tn/job/35/06.md

2.8 KiB

አጠቃላ መረጃ፡

ኤሊሁ ንግግሩን ቀጠለ፡፡

ኃጢአት ብትሰራ… በእርሱ ላይ ምን ታደርጋለህ/ትጨምራለህ?

እነዚህ ሁለት መስመሮች ተመሳሳይ ትርጉም ይጋራሉ፡፡ ሁተኛው መስመር የመጀመሪያውን መስመር ትርጉም ያጠናክራል፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ኃጢአት ብትሰራ፣ እግዚአብሔርን ምን ተጎዳዋለህ?

ኤሊሁ ይህንን ጥያቄ የሚያነሳው የኢዮብ ኃጢአት በእግዚአብሔር ላይ አንዳች ነገር እንደማያመጣ ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ "ኃጢአት ብትሰራ፣ እግዚአብሔርን አንዳች አትጎዳውም፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

መተላለፍህ ወደ ላይ ቢከመር፣ እርሱን ምን ታደርገዋለህ?

ኤሊሁ ስለ "መተላለፎች" የሚናገረው ቁሶች እንደሆኑ አድርጎ ነው፤ ብዙ መተላለፎችን ማድረግ ደግሞ እነዚህን ቁሶች አንዱን በሌላው ጫፍ ወደ ላይ መከመር እንደሆነ አድርጎ ይገልጻል፡፡ ይህንን ጥያቄ የሚጠይቀው ኢዮብ በመተላለፉ በእግዚአብሔር ላይ አንዳች ማምጣት ማድረግ እንደማይችል ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡ "አንተ ብዙ ታላላቅ መተላለፎችን ብትፈጽም፣ በእርሱ ላይ አንዳች ማድረግ አትችልም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚሉትን ይመልከቱ)

ጻድቅ ብትሆን፣ ለእርሱ ምን ልትሰጠው ትችላለህ? እርሱ ከአንተ እጅ ምን ይቀበላል?

ሁለቱ ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄዎች በመሰረቱ ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ናቸው፤ ሁለቱም የሚገልጹት የኢዮብ ጽድቅ ለእግዚአብሔር አንዳች ነገር እንደማይጨምር ነው፡፡ "አንተ ጻድቅ ብትሆን፣ ይህ አንተ ለእርሱ አንዳች ነገር እንድትሰጠው አያበቃህም፤ ደግሞም እርሱ ከአንተ እጅ የሚቀበለው አንዳች ነገር የለም፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ እና ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)

ከአንተ እጅ መቀበል

እዚህ ስፍራ "እጅ" የሚለው ቃል የሚወክለው ኢዮብን ነው፡፡ "ከአንተ እጅ መቀበል"

ሌላ የሰው ልጅ

"ሌላ የሰው ልጅ" ወይም "ሌላ ሰው"