am_tn/job/35/01.md

1.9 KiB

ይህ ፍትህ ነው… ‘በእግዚአብሔር ፊት ያለኝ መብት ነው' ብለህ ታስባለህ?

ኤሊሁ ኢዮብን ለመገዳደር ጥያቄዎችን ያነሳል፡፡ "አንተ ትክክል እንደሆንክ ታስባለህ… ‘በእግዚአብሔር ፊት መብቴ ነው'" ትላለህ ወይም "ይህ ልክ አይደለም…‘በእግዚአብሔር ፊት መብቴ ነው'" ትላለህ፡፡ በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ይህን በማለትህ ልክ የሆንክ ይመስልሃል

"አንተ ይህን ማለትህ ልክ ይመስልሃል"

ይመስልሃል/እንዲህ ታስባለህ

እዚህ ስፍራ "አንተ" የሚለው ነጠላ ቁጥር ሲሆን የሚያመለክተውም ኢዮብን ነው፡፡ (አንተ የሚለው ተውላጠ ስም መልኮች የሚለውን ይመልከቱ)

በእግዚአብሔር ፊት ያለኝ መብት

ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ኢዮብ በእግዚአብሔር ፊት ንጹህ መሆኑን እየተናገረ ነው፡፡ ወይም 2) ኢዮብ ከእግዚአብሔር ይልቅ እኔ ትክክል ነኝ እያለ ነው፡፡

አንተ ‘ይህ ለእኔ ምን ጥቅም አለው?' ብለህ ጠይቀሃል፡፡ ደግሞም፣ ‘ኃጢአት ባለመስራቴ ምን አተረፍኩ?' ብለሃል፡፡

ኤሊሁ ኢዮብ እነዚህን ሁለት ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄዎች እንዳነሳ ይጠቅሳል፡፡ "አንተ እንዲህ ብለሃል፣ ‘ይህ እኔን አልጠቀመኝም' ደግሞም፣ ‘ኃጢአት ብሰራ ከሚደርስብኝ ምንም የተሻለ አልሆነልኝም/ኃጢአት ባለመስራቴ አልተጠቀምኩም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)