am_tn/job/33/25.md

2.6 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኤሊሁ ከኢዮብ ጋር መነጋገሩን ቀጥሏል፡፡

ከዚያም

"ከዚይም" የሚለው ቃል እዚህ ስፍራ የዋለው እግዚአብሔር ለመላዕክቱ ጥያቄ ምላሽ ቢሰጥ ምን እንደሚሆን ለማመልከት ነው፡፡ "ከዚይም በውጤቱ" ወይም "መላዕክቱ ለእግዚአብሔር ከሚያቀርቡት ጥያቄ የተነሳ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

ስጋው ከትንሽ ልጅ ገላ ይልቅ አዲስ ይሆናል

ይህ የሚናገረው የተፈወሰው ሰው አካሉ እንደ ህጻን አካል ታድሰሶ ዳግም እንደሚታደስ ነው፡፡ "የታመመው ሰው አካል ዳግም እንደ ወጣት ሰው አካል ይታደሳል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ከልጅ ይልቅ ታድሶ

በዚህ ንጽጽር፣ "አዲስ" የሚለው ቃል ግነት ነው፡፡ "እንደ ልጅ አዲስ ገላ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ኩሸት እና አጠቃላይ አስተያየት የሚሉትን ይመልከቱ)

የልጅ

ይህ የሚያመለክተው የልጅን ገላ ነው፡፡ "የልጅ ገላ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የተተወ/የተዘለለ የሚለውን ይመልከቱ)

ወደ ወጣትነቱ ቀናት ጥንካሬ ይመለሳል

ይህ የሚናገረው ሰውየው ዳግም ወጣት እንደነበረበት ዘመኑ ጥንካሬ ያንኑ የወጣትነት ዘመኑን ብርታት እንደሚይዝ ነው፡፡ "ወጣት እንደነበረበት ዘመን ዳግም ብርቱ ይሆናል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

የእግዚአብሔርን ፊት በደስታ ይመለከታል

ይህ ፈሊጥ ነው፡፡ "በደስታ እግዚአብሔርን ያመልካል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

የእግዚአብሔር ፊት

እዚህ ስፍራ እግዚአብሔር የተገለጸው በ "ፊቱ" ነው፡፡ "እግዚአብሔር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

እግዚአብሔር ለሰው ድል ይሰጣል

"እግዚአብሔር ሰውን ያድናል" ወይም "እግዚአብሔር ለሰው ነገሮችን ዳግም ያስተካክላል"