am_tn/job/33/13.md

1.9 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኤሊሁ ከኢዮብ ጋር መነጋገሩን ቀጥሏል፡፡

ለምን እርሱን በመቃወም ትታገላለህ?

ኤሊሁ ይህንን ጥያቄ የሚጠቀምበት ኢዮብ ከእግዚአብሔር ጋር መታገል እንደሌለበት ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ ይህ ጥያቄ በዐረፍተ ነገር መልክ ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ከእግዚአብሔር ጋር መታገል የለብህም" ወይም "ከእግዚአብሔር ጋር ለመከራከር መሞከር የለብህም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይልከቱ)

እርሱ በሚያደርገው ሁሉ አይጠየቅም

"እርሱ የሚያደርገውን ማናቸውንም ነገር ለእኛ ማብራራት አይኖርበትም"

እግዚአብሔር በአንድም- በሌላም መንገድ ይናገራል

ይህ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው፡፡ "እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ደግሞ ደጋግሞ ይናገራል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በህልም… በምሽት በራዕይ

እነዚህ ሀረጎች አንድ አይነት ትርጉም አላቸው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

በሰዎች ላይ ከባድ እንቅልፍ ሲወድቅ፣ በአልጋ ላይ አንቀላፍተው ሳሉ

ይህ ሰዎች በከባድ እንቅልፍ ላይ ሳሉ፣ እንቅልፍ በእነርሱ ላይ እንደ ወደቀባቸው ወይም እነርሱን እንዳሸነፈ አድርጎ ይናገራል፡፡ "ሰዎች በአልጋቸው ላይ ተኝተው ሙሉ እንቅልፍ ወስዷቸው ሳለ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)