am_tn/job/31/29.md

2.2 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ የእግዚአብሔር ቅጣት እንደማይገባው ሁኔታዎችን መግለጹን ቀጥሏል፣ ይልቁንም፣ ጥፋት እንደሌለበት እና ንጹህ እንደሆነ ያውቃል፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)

እኔን የሚጠሉ ሁሉ በሚጠፉበት ጊዜ

"ጥፋት" የሚለው ረቂቅ ስም "ጠፋ" በሚለው ግስ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "እኔን የሚጠላ ማንም ቢሆን በሚጠፋበት ጊዜ" ወይም "እኔን በሚጠላ ማንም ሰው ክፉ ነገር በሚደርስበት ጊዜ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

እርሱን ጥፋት በሚውጠው ጊዜ

"ጥፋት ሲደርስበት"

እንዲህ ከሆነ/በዚይን ጊዜ በእኔ ላይ ክስ አቅርቡ

ይህ ሀረግ በመጀመሪያው ጽሁፉ በቀረበበት ቋንቋ ወይም በሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂዎች ውስጥ የለም፡፡ እዚህ የተጨመረው በኢዮብ ረዘም ያለ ንግግር ውስጥ ያለውን ሀሳብ ላለማጉደል ነው፡፡

በእርግጥ፣ አፌ እንኳን ኃጢአት እንዲናገር አልፈቀድኩም

እዚህ ስፍራ "አፌ/አንደበቴ" የሚለው የሚወክለው የኢዮብን ንግግር ነው፡፡ "በእውነት ራሴን ለኃጢአት አሳልፌ አልሰጠሁም" ወይም "በእውነት፣ ኃጢአት አልሰራሁም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

የእርሱ ህይወት እንዲረገም በመጠየቅ

እዚህ ስፍራ "የእርሱ ህይወት እንዲረገም በመጠየቅ" የሚለው የሚገልጸው አንድ ሰው እንዲሞት መራገምን ነው፡፡ "ይሞት ዘንድ እርሱን በመርገም" ወይም "ህይወቱን በመርገም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)