am_tn/job/31/26.md

2.5 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ የእግዚአብሔር ቅጣት እንደማይገባው ሁኔታዎችን መግለጹን ቀጥሏል፣ ይልቁንም፣ ጥፋት እንደሌለበት እና ንጹህ እንደሆነ ያውቃል፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)

የጨረቃ አካሄድ

እዚህ ስፍራ "አካሄድ" የሚወክለው ቀስ ብሎ መንቀሳቀስን ነው፡፡ "ጨረቃ ሰማይን እያቋረጠች ስትንቀሳቀስ"

ጨረቃ በድምቀቷ ስትራመድ

"ድምቀት" የሚለው ረቂቅ ስም "ብሩህ" ወይም "በብሩህነት" በሚሉ ቃላት ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ብሩኋ ጨረቃ ሰማይን እያቋረጠች ስትንቀሳቀስ" ወይም "ጨረቃ ብሩህ ሆና በሰማይ ስትንቀሳቀስ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

ልቤ በስውር ተስቦ ቢሆን

እዚህ ስፍራ "ልቤ" የሚለው የሚወክለው ኢዮብን ነው፡፡ ይህ ሀረግ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "በድብቅ ወደ እነርሱ ተስቤ ቢሆን" ወይም "በድብቅ እነርሱን ለማምለክ ፈልጌ ቢሆን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)

በዚህም ምክንያት አፌ እጄን ስሞ ቢሆን

እዚህ ስፍራ "አፌ" የሚለው የሚወክለው ኢዮብን ነው፡፡ ይህ የፍቅር እና የተመስጦ ምልክት ነው፡፡ "ስለዚህም እጄን ስሜ ቢሆን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትምዕርታዊ/ምልክታዊ ድርጊት የሚለውን ይመልከቱ)

እነርሱን ለማምለክ

"ፀሐይን እና ጨረቃን ለማምለክ"

በዳኞች መቀጣት

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "የትኛዎቹ ዳኞች እኔን ቢቀጡኝ ትክክለኛ ይሆናሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)

በሰማይ ያለውን አምላክ ክጄ ቢሆን

"በላይ ላለው እግዚአብሔር አምላክ ታማኝ ሳልሆን ቀርቼ ቢሆን"