am_tn/job/31/24.md

1.8 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ የእግዚአብሔር ቅጣት እንደማይገባው ሁኔታዎችን መግለጹን ቀጥሏል፣ ይልቁንም፣ ጥፋት እንደሌለበት እና ንጹህ እንደሆነ ያውቃል፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)

ወርቅን ተስፋ አድርጌ ቢሆን

"ተስፋ" የሚለው ረቂቅ ስም "ታመነ" ወይም "ተስፋ አደረገ" በሚለው ግስ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "በወርቅ ታምኜ ቢሆን" ወይም "የብዙ ወርቅ ባለቤት መሆን ይጠብቀኛል ብዬ ተስፋዬን ጥዬበት ቢሆን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

ምርጥ የሆነውን ወርቅ ‘የታመንኩት በአንተ ነው' ብዬው ቢሆን

ይህ ስንኝ/ቁጥር ከላይኛው ቁጥር ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

እጄ ብዙ ሀብት ነበረው

እዚህ ስፍራ "እጄ" የሚለው የሚገልጸው የኢዮብን ነገሮችን የማከናወን አቅም ነው፡፡ "በችሎታዬ ብዙ ሀብት አከማችቻለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

እንዲህ ከሆነ በእኔ ላይ ክስ አቅርቡ

ይህ ሀረግ በመጀመሪያው ጽሁፉ በቀረበበት ቋንቋ ወይም በሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂዎች ውስጥ የለም፡፡ እዚህ የተጨመረው በኢዮብ ረዘም ያለ ንግግር ውስጥ ያለውን ሀሳብ ላለማጉደል ነው፡፡