am_tn/job/31/19.md

3.1 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ የእግዚአብሔር ቅጣት እንደማይገባው ሁኔታዎችን መግለጹን ቀጥሏል፣ ይልቁንም፣ ጥፋት እንደሌለበት እና ንጹህ እንደሆነ ያውቃል፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)

ልቡ ባርኮኝ ካልሆነ

"ልቡ/የእርሱ ልብ" የሚለው ሀረግ የሚወክለው ልብስ የሚፈልገውን የተራቆተ ድሃ ነው፡፡ "እርሱ አመስግኞኝ/ባርኮኝ ካልሆነ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

ከበጎቼ ፀጉር ከተሸለተው ለብሶ ሞቆት ካልሆነ

እዚህ ስፍራ "የበጎቼ ፀጉር" የሚለው የሚገልጸው ከኢዮብ በጎች ፀጉር የተሰራን ብርድ ልብስ ወይም ልብስ ነው፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ከበጎቼ ሱፍ የተሰራው ልብስ ሳያሞቀው ቀርቶ ቢሆን" ወይም "ከበጎቼ ሲፍ የተሰራ ልብስ ሳልሰጠው ቀርቼ ቢሆን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)

አባት በሌላቸው ላይ እጆቼን አንስቼ ቢሆን

በአንድ ሰው ላይ እጅን ማንሳት ማለት ያንን ሰው መጉዳትን ይገልጻል፡፡ "አባት የሌላቸውን አግባብ የሌለው ሁኔታ አድርሼባቸው ቢሆን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

ድጋፌን በከተማ መግቢያ አይቻለሁ

እዚህ ስፍራ "ማየት" የሚለው "ማወቅ፣" ለሚለው ዘይቤ ሲሆን "ድጋፍ" የሚለው "ማረጋገጫ" ለሚለው ዘይቤ ነው፡፡ "የከተማ መግቢያ/በር" የሚለው ደግሞ በከተማዋ በር ለሚቀመጡ መሪዎች ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ/ ነው፡፡ "በከተማዋ በር የሚቀመጡ መሪዎች ስለ እኔ እንደሚመሰክሩ አውቃለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚሉትን ይመልከቱ)

በከተማይቱ በር

ይህ የከተማይቱ ታላላቅ ሰዎች ውሳኔ ለመስጠት የሚቀመጡበት ስፍራ ነው

በእኔ ላይ ክሳችሁን አቅርቡ

ይህ ሀረግ በመጀመሪያው ጽሁፉ በቀረበበት ቋንቋ ወይም በሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ቅጂዎች ውስጥ የለም፡፡ እዚህ የተጨመረው በኢዮብ ረዘም ያለ ንግግር ውስጥ ያለውን ሀሳብ ላለማጉደል ነው፡፡