am_tn/job/31/16.md

2.9 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ የእግዚአብሔር ቅጣት እንደማይገባው ሁኔታዎችን መግለጹን ቀጥሏል፣ ይልቁንም፣ ጥፋት እንደሌለበት እና ንጹህ እንደሆነ ያውቃል፡፡ ሀሳቡን በቁጥር 16 እና 17 ላይ አይጨርስም፡፡ ይልቁንም በቁጥር 18 ላይ እነዚህ ለምን ጥፋተኛ እንዳልሆነ ያብራራል፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)

ለድሆች የሚያስፈልጋቸውን ከልክዬ ከሆነ

"ድሆች የሚፈልጉትን እንዳያገኙ ከልክዬ ከሆነ"

የመበለቲቱ ዐይኖች በለቅሶ እንዲፈዙ አድርጌ ከሆነ

እዚህ ስፍራ "እየፈዘዙ እንዲሄዱ/እንዲፈዙ" የሚለው የሚያመለክተው መበለት ብዙ በማንባት ዐይኖቿ ሊፈዙ መቻላቸውን ነው፡፡ "አንዲት መበለት በታላቅ ሀዘን እንድታለቅስ ምክንያት ሆኜ ቢሆን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ቁራሼን

"ምግቤን"

ምክንያቱም ከልጅነቴ አንስቶ አባት ለሌላቸው እንደ አባት ሆኜ አሳድጌያለሁ

እዚህ ስፍራ "ወላጅ የሌላቸው" የሚለው የሚያመለክተው በአጠቃላይ ወላጆቻቸው ሞቱባቸውን ነው፡፡ ኢዮብ ወላጅ የሌላቸውን እንዴት ይረዳ እንደነበር ይናገራል፡፡ "ምክንያቱም ገና ወጣት ሳለሁ እንኳን ወላጅ የሌላቸውን እንደ አባት ሆኜ እንከባከባቸው ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የስማዊ ሀረግ ክፍል የሚለውን ይመልከቱ)

በወጣትነቴ ምክንያት

"ከእነዚህ ነገሮች ውስጥ አንዱንም አልፈጸምኩም" የሚለው ሀረግ ትርጉም ከአውዱ/አገባቡ ግልጽ ነው፡፡ "ነገር ግን ከእነዚህ ነገሮች ውስጥ አንዱንም አልፈጸምኩም፣ ምክንያቱም ከወጣትነቴ አንስቶ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የተተወ/የተዘለለ የሚለውን ይመልከቱ)

ከእናቴ ማህጸን አንስቶ መበለቲቱን ደግፌያለሁ

ኢዮብ መበለቶችን በእውነት እንዴት እንደ ደገፈ ይናገራል፡፡ "ከእናቴ ማህጸን አንስቶ" የሚለው ይህንን በህይወት ዘመኑ ሁሉ ማድረጉን በማጋነን ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ "ዘመኔን በሙሉ አባት የሌላቸውን ልጆች እናቶች ደግፌያለሁ" ወይም "ዘመኔን በሙሉ መበለቶችን ደግፌያለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ኩሸት እና አጠቃላይ አስተያየት የሚሉትን ይመልከቱ)