am_tn/job/31/13.md

1.6 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ የእግዚአብሔር ቅጣት እንደማይገባው ሁኔታዎችን መግለጹን ቀጥሏል፣ ይልቁንም፣ ጥፋት እንደሌለበት እና ንጹህ እንደሆነ ያውቃል፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)

ኢዮብ እነዚህን ጥያቄዎች የሚያነሳው እግዚአብሔር በእርሱ ላይ እንዲፈርድ የሚያደርግ በደል ሰርቶ ራሱን ንጹህ

አድርጎ እንደማያቀርብ በትኩረት ለመግለጽ ነው፡፡ "እንዲህ ቢሆን ኖሮ እግዚአብሔር ሊፈርድብኝ ሲመጣ ራሴን ለመከላከል የማቀርበው አንዳች ነገር አይኖርም ነበር፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

በማህጸን ያበጀኝ እነርሱንስ አላበጀምን? ሁላችንንም በማህጸን የሰራን እርሱ አይደለምን?

ኢዮብ እነዚህን ጥያቄዎች የሚያነሳው ከእርሱም አገልጋዮቹ እንደማይለይ በትኩረት ለመግለጽ ነው፡፡ አገልጋዮቹን ከራሱ ዝቅ አድርጎ ቢመለከት እግዚአብሔር እንደሚቆጣ ይናገራል፡፡ "በማህጸን የሰራኝ እርሱ፣ አነርሱንም ፈጥሯል፡፡ እርሱ ሁላችንንም በማህጸን ሰርቶናል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)