am_tn/job/31/07.md

2.8 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ የእግዚአብሔር ቅጣት እንደማይገባው ሁኔታዎችን መግለጹን ቀጥሏል፣ ይልቁንም፣ ጥፋት እንደሌለበት እና ንጹህ እንደሆነ ያውቃል፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)

እርምጃዎቼ ከመንገድ ፈቀቅ ብለው ቢሆን

እዚህ ስፍራ "እርምጃዎቼ" የሚለው የኢዮብን ባህርይ የሚገልጽ ዘይቤ ሲሆን "ከመንገድ ፈቀቅ ብለው ቢሆን" የሚለው ከትክክለኛ አኗኗር መውጣትን የሚያሳይ ዘይቤ ነው፡፡ "ከጽድቅ ህይወት ዘወር ብዬ ቢሆን" ወይም "ትክክለኛ የሆነውን ማድረግ አቁሜ ቢሆን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ልቤ ዐይኖቼን ተከትሎ ሄዶ ቢሆን

እዚህ ስፍራ "ልቤ" እና "ዐይኖቼ" የሚሉት ኢዮብ ለሚፈልጋቸው እና ለሚያያቸው ነገሮች ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ናቸው፡፡ ልብ ዐይንን ተከትሎ መሄድ የሚለው የተመለከተውን ለማድረግ መፈለግን የሚገልጽ ዘይቤ ነው፡፡ ይህ ኢዮብ የተመለከተውን በኃጢአት የተሞሉ ነገሮች ያመለክታል፡፡ "ከተመለከትኳቸው ክፉ ነገሮች አንዱን ለማድረግ ፈልጌ ቢሆን ኖሮ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት እና ዘይቤያዊ አነጋገር የሚሉትን ይመልከቱ)

በእጄ ላይ አንዳች በደል ተገኝቶ ቢሆን

ይህ ጥፋተኝነትን ለማመልከት የሚውል ዘይቤ ነው፡፡ "በአንዳች በደል ውስጥ ብገኝ ኖሮ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እንዲህ ቢሆን፣ እኔ የዘራሁትን ሌላው ይብላው፣ ደግሞም የተከልኩት ከስሩ ይነቀል

ኢዮብ በእርግጥ በደል ፈጽሞ ቢሆን እነዚህ ክፉ ነገሮች ይድረሱብኝ እያለ ነው፡፡ በደል ፈጽሞ ቢሆን ከባድ የሆነውን የመዝራት ተግባር በእርሻው ላይ ያከናውናል ነገር ግን ከዚያ አንዳች መቅመስ አይችልም፡፡

የተከልኩት ከስሩ ተነቅሎ ይጥፋ

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ሌላ ሰው መጥቶ ከእርሻዬ አዝመራዬን ይውሰድ፡፡ በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)