am_tn/job/31/05.md

1.5 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ መናገሩን ቀጥሏል፡፡

እንዲህ አድርጌ ቢሆን

በኢዮብ 31፡ 5-40 ውስጥ የእግዚአብሔር ቅጣት እንደሚይገባው የተለያዩ ሁኔታዎችን ይገልጻል፡፡ ይልቁንም፣ ጥፋት እንደሌለበት እና ንጹህ እንደሆነ ያውቃል፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)

በሀሰት መንገድ ተመላልሼ እንደሆነ፣ እግሮቼ ወደ ማታለል ፈጥነው እንደሆነ

እዚህ ስፍራ "መመላለስ" እና "መፍጠን" የሚሉት ኢዮብ እንዴት እንደኖረ የሚገልጹ ዘይቤዎች ናቸው፡፡ "አንዳች ሀሰት የሆነ ነገር አድርጌያለሁን ወይስ ይሁን ብዬ የፈጸምኩት ማታለል አለን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በትክክለኛ ሚዛን ልመዘን

ሰዎች ነገሮችን ለመለካት እና ዋጋቸውን ለመወሰን ሚዛን ይጠቀማሉ፡፡ ይህ ምስል በንጹህነት መበየንን ይወክላል፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "በንጹህነት ልመዘን" ወይም "እግዚአብሔር እንደ ንጽህናዬ ይፍረድብኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)