am_tn/job/31/01.md

3.1 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ መናገሩን ቀጥሏል፡፡

ከዐይኖቼ ጋር ቃል ኪዳን ገባሁ

ኢዮብ ዐይኖቹ ሰው የሆኑ ይመስል ስለሚመለከተው ነገር ከዐይኖቹ ጋር ቃል መግባቱን ይናገራል፡፡ "ስለምመለከተው ነገር ከዐይኖቼ ጋር ጽኑ ቃል ገባሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና ሰውኛ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)

ከዐይኖቼ ጋር ቃል ኪዳን ገባሁ

ኢዮብ ምን ቃል ኪዳን እንደገባ ግልጽ ተደርጎ ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ድንግሊቱን በአምንዝራ አይን እንዳልመለከት የጸና ኪዳን ገባሁ" ወይም "ወደ አንዲት ድንግል በአመንዝራነት ላለመመልከት ቃል ገባሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)

ታዲያ እንዴት ወደ አንዲት ድንግል በአመንዝራነት ፍላጎት እመለከታለሁ?

ኢዮብ ይህንን ጥያቄ የሚጠቀምበት ቃልኪዳኑን በምንም ምክንያት እንደማያፈርስ ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡ "ስለዚህ በእርግጥ ወደ አንዲት ድንግል በአመንዝራነት ዐይን አልመለከትም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ከላይ ከእግዘአብሔር ዘንድ ድርሻዬ፣ በከፍታ ካለው ሁሉን ቻይ ከሆነው ርስቴ ምንድን ነው?

ኢዮብ እግዚአብሔር ለሰዎች ባህሪ ያለውን ምላሽ የሚገልጸው እግዚአብሔር ለሰዎች የሚሰጠው ርስት ክፍል አድርጎ ነው፡፡ "በሰማይ የሚኖር አምላክ ለእኔ የሚመልሰው እንዴት ነው? በላይ የሚኖረው ሁሉን ቻይ አምላክ ምን ይፈጽማል? በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)

ከላይ ከእግዘአብሔር ዘንድ ድርሻዬ፣ በከፍታ ካለው ሁሉን ቻይ ከሆነው ርስቴ ምንድን ነው?

ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች፤ ኢዮብ እነዚህን ጥያቄዎች የተጠቀመባቸው ተከታዬቹን ነጥቦች ለማጉላት ነው 1) እግዚአብሔር መጥፎ ባህሪ ያለውን አይባርከውም፡፡ "ወደ አንዲት ሴት በአመንዝራነት ዐይን ብመለከት፣ በላይ በሰማይ የሚኖር ሁሉን ቻይ አምላክ አይባርከኝም፡፡" ወይም 2) እግዚአብሔር መጥፎ ባህርይን ይቀጣል፡፡ "ወደ ሴት በአመንዝራነት ብመለከት፣ በሰማይ የሚኖር ሁሉን ቻይ አምላክ በእርግጥ ይቀጣኛል፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)