am_tn/job/30/27.md

2.1 KiB

ልቤ ተጨነቀ እረፍት አላገኘም

ኢዮብ ልቡ ሰው እንደሆነ አድርጎ ይገልጻል፡፡ "በልቤ ታወክሁ/ተጨነቅሁ፣ ደግሞም መከራው ማብቂያ የለውም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

የመከራ ቀን መጣብኝ

የመከራ ቀን በኢዮብ ላይ መምጣቱ የሚወክለው ኢዮብ ለብዙ ቀናት በመከራ ውስጥ መቆየቱን ነው፡፡ "ለአያሌ ቀናት በመከራ ውስጥ ኖርኩ" ወይም "በየቀኑ መከራ ወረደብኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ኖርኩ/ቆየሁ

እዚህ ስፍራ "ኖርኩ/ቆየሁ" የሚለቀው የሚገልጸው በህይወት መቆየቱን ነው፡፡ "ኖርኩ" ወይም "አለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ፀሐይ ሳይመለከት፣ በጨለማ ውስጥ እንደሚኖር ሰው

እዚህ ስፍራ "በጨለማ ውስጥ መኖር" የሚለው አገላለጽ እጅግ ማዘንን የሚገልጽ ዘይቤያዊ አነጋገር ነው፡፡ "ነገር ግን ፀሐይን ሳይመለከት" የሚለው ሀረግ "በጨለማ ውስጥ መኖር" የሚለውን ፀሐይ ባለመውጣቷ ምከንያት ጨለማው አለመፈጠሩን የሚያብራራ ዘይቤ ነው፡፡ "እጅግ እንዳዘነ ሰው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

የቀበሮዎች ወንድም፣ የሰጎን ወዳጅ

የእነዚህ እንስሳት ወንድም መሆን እንደ እነርሱ አይነት መሆን ለሚለው ዘይቤያዊ አነጋገር ነው፡፡ "በበረሃ እንደሚጮሁ ቀበሮዎች እና ሰጎኖች ሆንኩ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)