am_tn/job/30/24.md

2.4 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኢዮብ ለእግዚአብሔር መናገሩን ቀጥሏል፡፡

ሲወድቅ እጆቹን አንስቶ የማይለምን አለን? በችግር የወደቀ ሰው ለእርዳታ አይጣራምን?

ኢዮብ እነዚህን ጥያቄዎች የሚያነሳው/የሚጠቀመው ለእርዳታ ወደ እግዚአብሔር መጮሁ ተገቢ መሆኑን ለማረጋገጥ ነው፡፡ "ማንም ሰው በችግር ላይ በሚወድቅበት ጊዜ ለእርዳታ ወደ እግዚአብሔር እጆቹን ያነሳል፡፡ በችግር ውስጥ የሚገኝ ሁሉ እርዳታ ለማግኘት ይጣራል፡፡" ወይም "እኔ ወድቄያለሁ፣ ስለዚህ እርዳታውን ስለምነው እግዚአብሔር እንደተሳሳትኩ ሊመለከተኝ አይገባውም፡፡ እኔ በመከራ ውስጥ እገኛለሁ፣ ስለዚህም በእርግጥ እርዳታ ለማግኘት እጣራለሁ!" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

በችግር …እኔ አላለቅስምን? ሰው… አያዝንምን?

ኢዮብ እነዚህን ጥያቄዎች የተጠቀመው ለሌሎች ጥሩ ነገሮችን ያደርግ እንደነበረ ለመናገር ነው፡፡ "እኔ እንደማለቅስ አንተ ታውቃለህ… የተቸገረ እና ያዘነ…ሰው!" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

መልካምን ነገር ተስፋ ሳደርግ፣ ክፉ ደረሰብኝ

መልካምን መጠባበቅ የሚገልጸው መልካም ነገሮችን ተስፋ ማድረግን ነው፣ ደግሞም የክፉ መድረስ/መምጣት የሚወክለው ክፉ ነገሮች እንደሚሆኑ ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ብርሃንን ተጠባበቅኩ… ጨለማ መጣብኝ/ሆነ

እዚህ ስፍራ "ብርሃን" የሚወክለው የእግዚአብሔርን በረከት እና ሞገስ ሲሆን "ጨለማ" ደግሞ የሚወክለው ችግርን እና መከራን ነው፡፡ "የእግዚአብሔርን ብርሃን በረከት ተጠባበቅሁ፣ ነገር ግን በምትኩ የጨለማ መከራ ደረሰብኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)