am_tn/job/30/22.md

1.5 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኢዮብ ለእግዚአብሔር መናገሩን ቀጥሏል፡፡

በነፋስ አነሳኸኝ… በማዕበል አናወጥከኝ

እነዚህ አገላለጾች የሚወክሉት እግዚአብሔር ኢዮብ ጸንቶ እንዲያልፍበት ያደረገውን እጅግ ከፍ ያለ መከራ ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እንዲያንገላታኝ አደረግህ

"ነፋሱ/ማዕበሉ እንዲገፋኝ አደረግህ"

ወደ ሞት ታደርሰኛለህ/ትገድለኛለህ

እዚህ ስፍራ "ወደ ሞት ታደርሰኛለህ" የሚለው የሚወክለው ኢዮብ እንዲሞት ማድረጉን ነው፡፡ "እንድሞት ታደርጋለህ/ትገድለኛለህ፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ህያው ለሆነው ሁሉ የተዘጋጀለት ቤት

ኢዮብ ይህ እግዚአብሔር ለህያዋን ነገሮች ሁሉ ይሄዱበት ዘንድ ያዘጋጀው ቤት ይህ እንደሆነ ስለ ሙታን ዓለም እየተናገረ ነው፡፡ "በህይወት የኖረ ሁሉ የሚሄድበት የሙታን ዓለም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ህይወት ያለው ነገር ሁሉ

ይህ፣ አንድ ቀን የሚሞት ነገር ግን አሁን በህይወት ያለ ነገር ሁሉ፡፡