am_tn/job/30/14.md

2.2 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኢዮብ እንደገና ስለሚሳለቁበት ሰዎች መናገሩን ቀጥሏል

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ ክፉ የሚያደርጉበትን ፌዘኞች በቡድን እንደሆኑ እና እንደ ሰራዊት በአንድላይ ሆነው እንደሚያጠቁት አድርጎ ይገልጻል፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በአንዲት ከተማ ትልቅ የቅጥር ፍራሽ/ብስ አልፎ እንደሚገባ ሰራዊት በእኔ ላይ መጡብኝ

ይህ የሚገልጸው ኢዮብን በሃይል ማጥቃታቸውን ነው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

በላዬ በሃይል መጡብኝ

ይህ የሚገልጸው ታላቅ የውቅያኖስ ማዕበል በእርሱ ላይ እንደመጣበት ብዙ ሆነው በአንድነት መጥተው እንዳጠቁት ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ፍርሃት በላዬ ወረደ/መጣ

ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ኢዮብ እጅግ ፈራ ወይም 2) ኢዮብ ኢንዲፈራ የሚያደርጉ ነገሮች እየሆኑ ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በነፋስ ተጠርጎ እንሚወሰድ ክብሬ ተወሰደ

ኢዮብ ነፋስ በድንገት ጠርጎ እንደወሰደው ነገር ክብሩ ከእርሱ መወሰዱን ይናገራል፡፡ "ማንም እኔን አያከብርም" ወይም "እኔ አሁን ማንም የማያከብረው ሰው ሆኛለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ብልጽግናዬ/ሀብቴ እንደ ደመና አለፈ

ኢዮብ የሃብቱን መጥፋት በነፋስ እንደተጠረገ ደመና ይገልጻል፡፡ እዚህ ስፍራ "ሀብት/ብልጽግና" ደህንነትን ወይም ጥበቃን ሊያመለክት ይችላል፡፡ "ከእንግዲህ አንዳች የለኝም" ወይም "ከእንግዲህ ሰላም አይደለሁም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)