am_tn/job/30/12.md

2.9 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኢዮብ እንደገና ስለሚሳለቁበት ሰዎች መናገሩን ቀጥሏል

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ ክፉ የሚያደርጉበትን ፌዘኞች በቡድን እንደሆኑ እና እንደ ሰራዊት በአንድላይ ሆነው እንደሚያጠቁት አድርጎ ይገልጻል፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በቀኜ ጀሌዎች ተነሱብኝ

"በቀኜ ጀሌዎች ተነሱብኝ" የሚለው በሚከተሉት መንገዶች ሊተረጎም ይችላል 1) በኢዮብ ቀኝ እጅ ላይ መነሳት በእርሱ ጥንካሬ ላይ መነሳትን ሊወክል ይችላል፡፡ "ወሮበሎች አቅሜን መቱት/አጠቁኝ" ወይም በኢዮብ ቀኝ እጅ ላይ መነሳት የእርሱን ክብር ማጥቃትን ይወክላል፡፡ "ጀሌው ክብሬን አጠፋ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት እና ዘይቤያዊ አነጋገር የሚሉትን ይመልከቱ)

አሳደዱኝ

"እንድሸሽ አስገደዱኝ"

የዐፈር ድልድል አዘጋጁብኝ

ሰራዊት አንዲትን ከተማ በቅጥሯ ላይ ተንጠላጥሎ ወጥቶ ለማጥቃት በቅጥሩ ስር አፈር ይከምራል፡፡ ኢዮብ በእርሱ ላይ የሚያፌዙት እንዲህ ያለ ነገር እንዳደረጉ ይናገራል፡፡ "ሰራዊት አንዲትን ከተማ ለማጥቃት እንደሚዘጋጅ እነርሱ እኔን ለማጥቃት ተዘጋጁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

መንገዴን ደመሰሱ

ይህ የሚገልጸው ኢዮብ ከጥቃታቸው እንዳያመልጥ ማድረጋቸውን ነው፡፡ "ከእነርሱ እንዳላመልጥ ከለከሉኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ጥፋትን ወደ እኔ አመጡ

እዚህ ስፍራ "ክፋትን ማምጣት" የሚለው የሚገልጸው ጥፋት እንደሆን ማድረግን ነው፡፡ "በእኔ ላይ ጥፋት እንዲደርስ ተጣጣሩ" ወይም "እኔን ለማጥፋት ሞከሩ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ማንም ሊያግዳቸው/ወደ ኋላ ሊመልሳቸው የማይችላቸው ሰዎች

እዚህ ስፍራ "ወደ ኋላ መመለስ/ማገድ" የሚለው የሚገልጸው አንድ ነገር እንዳያደርጉ እነርሱን መከልከልን/ማስቆምን ነው፡፡ "እኔን ከማጥቃት ማንም የማያስቆማቸው ሰዎች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)