am_tn/job/30/09.md

2.8 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኢዮብ እንደገና ስለሚሳለቁበት ሰዎች መናገሩን ቀጥሏል ነገር ግን አሁን ለሚያንጓጥጥ ዘፈናቸው ሆኛለሁ "ዘፈን" የሚለው ረቂቅ ስም "ዘፈነ" በሚል ግስ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "በእኔ ላይ ለማንጓጠጥ ይዘፍናሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

ለእነርሱ መተረቻ ሆኛለሁ

እዚህ ስፍራ "መተረቻ" የሚለው ሰዎች በጭከና ለማፌዛቸው ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት ነው፡፡ "አሁን እነርሱ በጭካኔ የሚዘባበቱብኝ ሆኛለሁ" ወይም "ስለ እኔ በፌዝ ጭካኔ የተሞላበት ነገር ይናገራሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

በፊቴ ላይ ምራቃቸውን ጢቅ ለማለት ወደኋላ አይሉም

ይህ በአዎንታዊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "በፊቴ ላይ አንኳን ይተፉብኛል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ምጸት የሚለውን ይመልከቱ)

እግዚአብሔር ከእኔ ቀስቴን ሰብሮታል

የተሰበረ ቀስት ጥቅም የለውም፡፡ "ቀስቴን ሰብሮታል" የሚለው ሀረግ ኢዮብን አቅመቢስ ስለ ማድረግ ዘይቤያዊ አገላለጽ ነው፡፡ "እግዚአብሔር እራሴን እንዳልከላከል አቅሜን ከእኔ ወስዶታል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በእኔ ላይ የሚያላግጡት

"በእኔ የሚቀልዱ"

በፊቴ ያለገደብ ክፉ ያደርጋሉ

ገደብ አንድ ሰው በነጻነት አንዳይንቀሳቀስ እና የሚፈልገውን እንዳያደርግ ያግዳል፡፡ እዚህ ስፍራ "መቆጠብ" የሚለው የሚገልጸው አንድ ነገር ከማድረግ መገታተትን፣ ሲሆን "ገደብን መስበር" የሚለው ደግሞ አንድ ነገር ከማድረግ አለመከልከልን ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ፌዘኞቹ በኢዮብ ላይ ክፉ ነገርን ከማድረግ አልተቆጠቡም፡፡ "ለእኔ ክፉ ከመሆን አልተገቱም" ወይም "በእኔ ላይ ማድረግ የሚፈልጉትን የጭካኔ ተግባር ሁሉ ያደርጋሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚሉትን ይመልከቱ)