am_tn/job/30/07.md

3.2 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኢዮብ ስለሚሳለቁበት ሰዎች አባቶች መናገሩን ቀጥሏል

እንደ አህዮች ያናፉ ነበር

ኢዮብ በረሃብ ይጮሁ የነበሩ ሰዎችን ከፍ ያለ ድምጽ እንደሚያሰሙ የሜዳ አህዮች ይገልጻቸዋል፡፡ "ከረሃባቸው የተነሳ እንደ ሜዳ አህያ ይጮሁ ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤያዊ የሚለውን ይመልከቱ)

በሳማ ስር በአንድነት ይሰባሰቡ ነበር

"ሳማ" ሹል እሾህ ያለው እጅብ ብሎ የሚበቅል ተክል ነው፡፡ ይህ የሚያመለክተው ቤት እንደሌላቸው ነው፡፡

የማይረቡ ሰዎች ልጆች ናቸው

እዚህ ስፍራ "የማርረቡ ሰዎች ልጆች" የሚለው የሚገልጸው የማይረባ/ጅል ባህሪይ እንዳላቸው ነው፡፡ "እንደ ጅሎች ነበሩ" ወይም "ሞኞች ነበሩ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በእርግጥ፣ ስም የለሽ ሰዎች ልጆች ነበሩ

"በእርግጥ" የሚለው ቃል ቀጥሎ የሚመጣውን ሀሳብ የሚያጠናክር ነው፡፡ እዚህ ስፍራ " የስም የለሽ ሰዎች ልጆች" የሚለው የሚገልጸው ስም እዚህ ግባ የሚባል ባህሪ እንዳሌላቸው ነው፡፡ "በእርግጥ፣ የሚረቡ ሰዎች አልነበሩም" ወይም "በእርግጥ፣ እርባና ቢስ ሰዎች ነበሩ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ስም የለሽ ሰዎች

እዚህ ስፍራ "ስም የለሽ" የሚለው የሚገልጸው አንዳች ክብር ወይም ከበሬታ የሌለው ማለት ነው፡፡ ይህ ማለት እርባና ቢስ ነበሩ ማለት ነው፡፡ "እርባና ቢስ ሰዎች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በአለንጋ እየተገረፉ ከምድሪቱ ይባረሩ ነበር

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ ለዚህ ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) አለንጋ የሚለው እንደ ወንጀለኛ ይቀጡ እንደነበር ያመለክታል፡፡ "ሰዎች እንደ ወንጀለኞች ይመለከቷቸው እና ከአገራቸው በግድ ያስወጧቸው ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ ወይም 2) ሰዎች በአለንጋ እየገረፉ በግድ ያስወጧቸው ነበር፡፡ "ሰዎች ይገርፏቸው እና ምድሪቱን ለቀው እንዲወጡ ያስገድዷቸው ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

ከምድሪቱ ይባረሩ ነበር

እዚህ ስፍራ "ምድሪቱ" የሚለው የሚያመለክተው ወደ በረሃ ከመሰደዳቸው አስቀድሞ የሚኖሩበትን ምድር ነው፡፡