am_tn/job/29/17.md

2.1 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ከቁጥር/ስንኝ 18-20 ባለው ክፍል ኢዮብ በእርሱ ላይ መከራ ከመድረሱ በፊት ይናገራቸው ስለነበሩ ነገሮች ይገልጻል፡፡

የ… መንጋጋ እሰብር ነበር፣ …ምርኮኞችን ነጻ አወጣ ነበር

ኢዮብ ኃጢአተኞችን በጥርሳቸው ያደኑትን እንደሚነክሱ የዱር አራዊት ይገልጻቸዋል፡፡ "አንድ ሰው የዱር አውሬን መንጋጋ ሰብሮ ያደነውን ከጥርሶቹ መሃል እንደሚያስጥለው፣ እኔም ኃጢአተኞች ሰዎችን እንዳያሳድዱ እከልክላቸው ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በጎጆዬ ውስጥ እሞታለሁ

እዚህ ስፍራ "ጎጆ" የሚወክለው የኢዮብን ቤት እና ቤተሰብ ነው፡፡ ኢዮብ እርሱን እንደ ወፍ ልጆቹን ደግሞ እንደ ወፍ ጫጩቶች አድርጎ ይናገራል፡፡ "ከቤተሰቦቼ ጋር በቤቴ ውስጥ እሞታለሁ" ወይም "በቤቴ በሰላም እሞታለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እድሜዬን እንደ ምድር አሸዋ አበዛለሁ

በወንዝ ዳርቻ ማንም ሊቆጥረው የማይችለው አሸዋ አለ፡፡ ማንም ሊቆጥረው ከሚችለው በላይ እድሜ እኖራለሁ ማለቱ ረጅም እድሜ እንደሚኖር አጋኖ መናገሩ ነው፡፡ "በጣም ዘመን እኖራለሁ" ወይም "ብዙ አመታት እኖራለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ኩሸት እና አጠቃላይ አስተያየት እንዲሁም ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)

የእኔ ስር… የእና ቅርንጫፍ

ኢዮብ ስለ ጥንካሬው በሚገባ ውሃ እንዳገኘ ዛፍ አድርጎ ይናገር ነበር፡፡ በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)