am_tn/job/29/14.md

2.1 KiB

ጽድቄን አበዛለሁ፤እንደልብስ ይሸፍነኛል

ብዙውን ጊዜ ሰዎች ጽድቅን እንደ ልብስ አድርገው ይገልጽዋታል፡፡ "ጽድቅ የሆነውን አደርግ ነበር፣ እርሷም ለእኔ እንደ ምለብሰው ልብስ ነበረች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ፍርዴ እንደ ልብስ እና እንደ ጥምጥም ነበረች

ብዙውን ጊዜ ሰዎች ጽድቅን እንደ ልብስ አድርገው ይገልጽዋታል፡፡ "ትክክል የሆነውን አደርግ ነበር፣ ፍትህ በእኔ ላይ እንደ ልብስ እና እንደ ጥምጥም ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤያዊ የሚለውን ይመልከቱ)

ጥምጥም

ወንዶች በራሳቸው ላይ የሚጠመጥሙት እና እንደ ኮፍያ የሚያደርጉት ረጅም ጨርቅ

ለዐይነ ስውራን ዐይን ነበርኩ

ይህ የሚወክለው ዐይነ ስውር የሆኑ ሰዎችን መርዳትን ነው፡፡ "ለዐይነ ስውራን ዐይን ነበርኩ" ወይም "ዐይነ ስውራንን እመራ ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ለአንካሶች እግር ነበርኩ

ይህ አካል ጉዳተኞችን መርዳትን ያመለክታል፡፡ "ለአንካሶች እግር ነበርኩ" ወይም "አንካሶችን እደግፍ ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ለችግረኞች አባት ነበርኩ

እዚህ ስፍራ "አባት ነበርኩ" የሚለው የሚወክለው ለሰዎች የሚያስፈልጋቸውን ማቅረብን ነው፡፡ "አባት ለልጆቹ የሚያስፈልጋቸውን እንደሚያቀርብ ለችግረኞች አቀርብላቸው ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)