am_tn/job/29/11.md

2.4 KiB

ጆሯቸው እኔን ካደመጠ በኋላ … ዐይናቸው እኔን ካደመጠ በኋላ

ጆሮዎች የሚለው የሚወክለው እርሱን የሰሙትን ሰዎች ሲሆን፣ ዐይኖች የሚለው ደግሞ የሚወክለው እርሱን ያዩተን ሰዎች ነው፡፡ "የነገርኳቸውን ከሰሙ በኋላ… እኔን ከተመለከቱ በኋላ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

ለእኔ ምስክርነት ይሰጡ፤ ደግሞም ያልኩትን ይቀበሉ ነበር

"የተናገርኩት ትክክል ነው በማለት ይመሰክሩ ነበር"

ድሃው ሲጮህ ካለበት ሁኔታ አወጣው ነበር

እዚህ ስፍራ "ድሃ የሆነው/ድሃው" የሚለው የሚያመለክተው ማንኛውንም ድሃ ሰው ነው፡፡ "ድሆች ሲጮሁ ደርሼ ካሉበት ችግር አወጣቸው ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የስማዊ ሀረግ ክፍል የሚለውን ይመልከቱ)

በሞት አፋፍ ላይ የደረሰው መርቆኛል

የአንድ ሰው ምርቃት/በረከት ወደ ሌላው መድረሱ የሚወክለው ያ ሰው ሌላውን መባረኩን ነው፡፡ "ሞት አፋፍ ላይ ደርሶ ነበረው ስረዳው ይባርከኝ ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በሞት አፋፍ ላይ የደረሰው/ለመጥፋት የተቃረበው

ይህ የሚወክለው ሊሞት የተቃረበውን ማናቸውንም ሰው ነው፡፡ "ሊሞቱ የተቃረቡ/በሞት አፋፍ ላይ ያሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የስማዊ ሀረግ ክፍል የሚለውን ይመልከቱ)

የመበለቶች ልብ በሀሴት እንዲዘምር አድርጌያለሁ

እዚህ ስፍራ "የመበለቶች ልብ" የሚለው የሚወክለው ማንኛይቱንም መበለት ነው፡፡ "መበለቶች በደስታ እንዲዘምሩ ምክንያት ሆኛለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ እና የስማዊ ሀረግ ክፍል የሚሉትን ይመልከቱ)