am_tn/job/28/12.md

3.1 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

በኢዮብ 28፡12-28 እውቀት እና ግንዛቤ ማግኘት በአንድ ስፍራ የሚገኙ እና ሰዎች የሚፈልጓቸው ውድ ሀብቶች እንደሆኑ ተደርጎ ተገልጽዋል፡፡ እውቀት እና ግንዛቤ ማግኘት የሚወክሉት ብልህ መሆንንና ነገሮችን በሚገባ መረዳትን መማርን ነው፡፡ በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ጥበብ ከወዴት ይገኛል? የመረዳትስ ስፍራው የት ነው?

እነዚህ ጥያቄዎች ተመሳሳይ ነገር ማለት ናቸው፤ የዋሉትም ጥበብን እና መረዳትን ማግኘት በጣም አስቸጋሪ መሆኑን ለማሳየት ነው፡፡ "ጥበብን እና መረዳትን ማግኘት በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ እና ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚሉትን ይመልከቱ)

ጥበብ ከወዴት ይገኛል?የመረዳትስ ስፍራው የት ነው?

ብልህ መሆን እና ግንዛቤ ማግኘት የተገለጹት ጥበብን እና መረዳትን እንደ ማግኘት ተደርጎ ነው፡፡ "ሰዎች ብልህ የሚሆኑት እንዴት ነው? ሰዎች ነገሮችን በሚገባ መረዳት የሚችሉት እንዴት ነው?" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ሰው ዋጋዋን አያውቅም

ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ጥበብ የተገለጸችው ሰዎች ሊገዟት እንደሚችሉት ነገር ተደርጋ ነው፡፡ "ሰዎች የሚረባው ምን እንደሆነ አያውቁም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ ወይም 2) "ዋጋ" ተብሎ የተተረጎመው ቃል "ስፍራ" ማለት ነው፡፡ "ሰዎች የት እንደምትገኝ አያውቁም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በህያዋን ምድር አትገኝም

"እናም በህያዋን ምድር አትገኝም፡፡" የህያዋን ምድር" የሚለው የሚያመለክተው ሰዎች የሚኖሩበትን ይህንን ምድር ነው፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "እናም ማንም በዚህ ምድር ጥበብን ሊያገኝ አይችልም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)

ጥልቅ ውኆች… ‘በእኔ ውስጥ አትገኝም' ይላሉ፤ ባህር ‘በእኔ ውስጥ አትገኝም' ይላል፡፡

ጥልቅ ውኆች እና ባህር የቀረቡት መናገር እንደሚችል ሰው ተደርገው ነው፡፡ "ጥበብ ከምድር በታች ባለው በጥልቅ ውኆች ውስጥ አትገኝም፣ አሊያም በባህር ውስጥ አይደለችም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)