am_tn/job/26/13.md

2.5 KiB

በእስትንፋሱ ሰማያትን ያነጻል

"እስትንፋስ" የሚለው ስም "ተነፈሰ" ወይም "እፍ አለ" በሚለው ግስ ሊተረጎም ይችላል፡፡ ይህ ምሳሌ የሚወክለው እግዚአብሔር ደመናትን ለመበተን እግዚአብሔር ነፋሳትን እንደሚያነፍስ ነው፡፡ "እግዚአብሔር ሰማያት ንጹህ ይሆኑ ዘንድ ደመናዎችን ይበትናል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እጆቹ በራሪውን አውሬ ወጋ

ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔር በእጆቹ ሰይፍ እንደ ያዘ እና እዚህ ስፍራ "የእርሱ እጅ" የሚለው ደግሞ የሚያመለክተው ያንን ሰይፍ ነው፡፡ "በሳው" መግደልን ያሳያል፡፡ "በሰይፉ በራሪ አውሬውን ወጋ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ እና ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚሉትን ይመልከቱ)

በራሪው አውሬ

"አውሬው ከእርሱ ለማምለጥ በሞከረ ጊዜ፡፡" ይህ በውሃ ውስጥ የሚኖረውን ረአብን ያሳያል፡፡ ኢዮብ 26፡12 ይመልከቱ፡፡

እነሆ፣ ይህ የመንገዱ ዘርፍ ነው

እዚህ ስፍራ "ዘርፍ" የሚወክለው ትልቅ ከሆነ ነገር ውስጥ አነስተኛ የሆነውን ክፈል ነው፡፡ "እነሆ፣ እነዚህ እግዚአብሔር የሰራቸው ነገሮች የሚያመለክቱት ከታላቅ ሀይሉ ውስጥ ጥቂቱን ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ከእርሱ ምንኛ ታናሽ ሹክሹክታውን እንሰደማለን!

ይህ እኛ ስለመኖሩ እንኳን ከነጭርሱ የማናውቀው የኢዮብን አድናቆት አጋኖ የሚገልጽ እግዚአብሔር ከሰራቸው ታላላቅ ነገሮች አንዱ ነው፡፡ እግዚአብሔር ያደረገውን ማየት የተገለጸው የእግዚአብሔርን ድምጽ እንደመስማት ተደርጎ ነው፡፡ "ይህ የእርሱን ጸጥ ያለ ማንሾካሾክ እንደመስማት ነው!" (ቃለ አጋኖ እና ዘይቤያዊ አነጋገር የሚሉትን ይመልከቱ)