am_tn/job/26/01.md

2.2 KiB

አቅም የሌለውን ክንድ … እርሱን እንዴት ረዳኸው

በዚህ ዐረፍተ ሀሳብ፣ ኢዮብ በልዳዶስን እየነቀፈው/እየከሰሰው ነው፡፡ "እርሱን" የሚለው የሚያመለክተው ኢዮብን ነው፡፡ "ክንድ" የሚለው ቃል ደግሞ የሚወክለው በአጠቃላይ ሰውየውን ነው፡፡ "እኔ አቅም የለኝም፤ ደግሞም አንዳች ጥንካሬ የለኝም፣ ነገር ግን አንተ እንደረዳኸኝ ያህል ትሆናለህ፣ ነገር ግን በእርግጥ አንተ ምንም አልረዳኸኝም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ምፀት እና ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚሉትን ይመልከቱ)

ጥበብ የሌለውን እንዴት መከርከው፤ እንዴት ጠቃሚነት ያለው እውቀት ሰጠው

ኢዮብ በልዳዶስ መልካም ምክር እና እውቀት እንዳልሰጠው እየተናገረ ነው፡፡ "አንተ የሚምልህ እኔ አንዳች ጥበብ እንሌለኝ እና አንተ እንደመከርከኝ፤ ደግሞም ጥሩ ምክር እንደሰጠኸኝ ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ምፀት የሚለውን ይመልከቱ)

ለእርሱ ተሰሚነት ያለው እውቀት ሰጠው

"ጥሩ ምክር ሰጠው"

እነዚህን ቃላት በማን እርዳታ ተናገርክ? አንተ…ይህ የማን መንፈስ ነበር?

በእነዚህ ጥያቄዎች ኢዮብ በበልዳዶስ ላይ መሳለቁን ይቀጥላል፡፡ ሁለቱም ጥያቄዎች ቃለ ምልልሳዊ ናቸው፤ ትርጉማቸውም በመሰረታዊነት አንድ ነው፡፡ በአንድነት የቀረቡት አንዱ ሀሳብ ሌላውን ለማጠንከር ነው፡፡ "እነዚህን ቃላት እንድትናገር እርዳታ ሳታገኝ አልቀረህም፡፡ ምናልባት እነዚህን ነገሮች እንድትናገር አንድ መንፈስ ሳይረዳህ አልቀረም!" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)