am_tn/job/25/04.md

3.3 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

በልዳዶ መናገሩን ቀጥሏል

ታዲያ ሰው እንዴት… በእግዚአብሔር ፊት…? ከ…የተወለደ ሰው እርሱ እንዴት?

እነዚህ ሁለት ጥያቄዎች በአንድነት የዋሉት ሰው በእግዚአብሔር ፊት ፍጹም ሊሆን እንደማይችል አጉልቶ ለመግለጽ ነው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ እና ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚሉትን ይመልከቱ)

ሰው እንዴት በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ሆኖ ሊገኝ ይችላል?

በውስጠ ታዋቂነት የሚሰጠው ምላሽ አይችልም የሚል ነው፡፡ "አንድ ሰው በፍጹም በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ሊሆን አይችልም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ከ.. የተወለደ … በእርሱ ፊት እንዴት ተቀባይነት ያገኛል?

በውስጠ ታዋቂነት የጥያቄው ምላሽ አይችልም የሚል ነው፡፡ "ከሴት የተወለደ ሰው በእግዚአብሔር ፊት በፍጹም ንጹህ ሊሆን ወይም ተቀባይነት ሊያገኝ አይችልም" (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ከሴት የተወለደ እርሱ/ሰው

ይህ ፈሊጣዊ አነጋገር ሁሉንም ሰው ያካትታል፡፡ "ማንኛውም ሰው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እነሆ

እዚህ ስፍራ "እነሆ" የሚለው ቃል ተከትሎ በሚመጣው ላይ ትኩረት ይጨምራል፡፡ "በእርግጥ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

በእርሱ ፊት ጨረቃ ብሩህነት የላትም

"ብሩህ" የሚለው ረቂቅ ስም በቅጽል መልክ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "በእግዚአብሔር ፊት ጨረቃ በቂ ብሩህነት የላትም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

በእርሱ እይታ ከዋክብት ንጹሃን አይደሉም

እዚህ ስፍራ "ንጹህ" ማለት ፍጹም ማለት ነው፡፡ "እርሱ ከዋክብትን እንኳን ፍጹም አድርጎ አያያቸውም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

ትል የሆነ፣ የሰው ልጅ … ሰው ምን ያህል ያንሳል

እነዚህ ሁለት መስመሮች ተመሳሳይ ነገር ይናገራሉ፤ በአንድነት ሆነው የሚያጎሉትም ሰው ፍጹም አለመሆኑን ነው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ትል ማን ነው

በልዳዶስ የሰው ልጆች እንደትሎች እርባና ቢስ መሆናቸውን ይገልጻል፡፡ "እንደ ትል እርባና ቢስ የሆነ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

የሰው ልጅ

ይህ ሰው የተገለጸበት ሌላ መንገድ ነው፡፡ "አንድ ሰው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)