am_tn/job/25/01.md

2.2 KiB

ሹሐዊው በልዶስ

ይህ የወንድ ስም በኢዮብ 2፡11 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ

ገናንነት እና መፈራት የእርሱ ናቸው

እዚህ ስፍራ "እርሱ" የሚለው የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው፡፡ "ገናና/የበላይ" እና "ፍርሃት" የሚሉት ረቂቅ ስሞች በግስ መልክ ሊጻፉ ይችላሉ፡፡ "እግዚአብሔር በሁሉም ላይ ይገዛል፣ እናም ሰዎች እርሱን ብቻ ይፍሩት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

እርሱ በሚገኝበት በከፍታ ስፍራ በላይ በሰማይ ስርአትን አበጅቷል

"በላይ በሰማይ ሰላምን አድርጓል"

ለሰራዊቱ ቁጥር ልክ/መጠን አለውን?

በልዳዶስ ይህንን ጥያቄ የተጠቀመው እግዚአብሔር ምን ያህል ታላቅ እንደሆነ አጉልቶ ለመግለጽ ነው፡፡ በውስጠ ታዋቂነት ለጥያቄው የተሰጠው ምላሽ "የለውም" የሚል ነው፡፡ ይህ የሚያመለክተው የእግዚአብሔር ሰራዊት የሆኑተን መልአክትን ነው፡፡ "በእርሱ ሰራዊት ውስጥ የመላዕክቱ ቁጥር መጠን የለውም፡፡" ወይም "የእርሱ ሰራዊቶች ማንምሊቆጥራቸው የማይቻለው እጅግ ብዙ ናቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ እና ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚሉትን ይመልከቱ)

የእርሱ ብርሃን የማያበራው በማን ላይ ነው?

በልዳዶስ ይህንን ጥያቄ የተጠቀመው እግዚአብሔር ለሁሉም ሰው ብርሃን እንደሚሰጥ አጉልቶ ለመግለጽ ነው፡፡ "የእርሱ ብርሃን በላዩ የማያበራለት ማንም የለም" ወይም "እግዚአብሔር ብርሃኑ በሁሉም ላይ እንዲበራ አድርጓል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)