am_tn/job/24/01.md

1.6 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኢዮብ መናገሩን ቀጥሏል

ሁሉን ቻይ በሆነው አምላክ የክፉ ሰዎች የፍርድ ጊዜ ለምን አይወሰንም

ኢዮብ ይህንን ጥያቄ የተጠቀመው እግዚአብሔር በክፉዎች ላይ አይፈርድም የሚለውን መረበሹን ለመግለጽ ነው፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር በክፉ ሰዎች ላይ ሚፈርድበትን ጊዜ ለምን እንደማይወስን አይገባኝም" ወይም "ሁሉን ቻይ የሆነው በክፉ ሰዎች ላይ መቼ እንደሚፈርድ መወሰን አለበት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)

ለእግዚአብሔር ተማኝ የሆኑ ለምን የፍርዱ ቀን ሲመጣ/ ሲደርስ አይመለከቱም?

ኢዮብ ይህንን ጥያቄ የተጠቀመው ጻድቃን እግዚአብሔር በኃጢአተኞች ላይ ሲፈርድ ባለመመልከታቸው የሚሰማቸውን መረበሽ ለመግለጽ ነው፡፡ "እርሱን የሚታዘዙ እርሱ በኃጢአተኞች ላይ ሲፈርድ የሚመለከቱ አይመስልም" ወይም "እግዚአብሔር በኃጢአተኞች ላይ ሲፈርድ እርሱን የሚያውቁ ይህንን የሚመለከቱበትን ቀን ማሳየት/ማምጣት አለበት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)