am_tn/job/23/15.md

1.5 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኢዮብ መናገሩን ቀጥሏል

አጠቃላይ መረጃ፡

እነዚህ እያንዳንዳቸው ሀረጋት ኢዮብ በዚያ ያደረጋቸውን ዋና ዋና ነጥቦች ለማጉላት የትይዩ ንጽጽር ዘይቤ መልኮች አላቸው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ ሚለውን ይመልከቱ)

ልቤን ደካማ አደረገው

ልቡ የደከመ ሰው ድንጉጥ ወይም በፍርሃት የተሞላ ነው፡፡ "እንድፈራ አደረግኸኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በጨለማ ወደ ፍጻሜ አልመጣሁም

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ ለዚህ ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) "ከፊቴ ያለው ድቅድቁ ጨለማ ዝም አላሰኘኝም" ወይም 2) "ጨለማ አላስቆመኝም" ወይም " እግዚአብሔር እንጂ ጨለማ አላስቆመኝም፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)

የፊቴ ትካዜ

እዚህ ስፍራ ኢዮብ ራሱን የሚገልጸው በ"ፊቱ/ገጹ" ነው፡፡ "ትካዜዬ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)