am_tn/job/23/10.md

2.7 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኢዮብ መናገሩን ቀጥሏል

እርሱ እኔ የምወስደውን መንገድ ያውቃል

የኢዮብ ድርጊቶች የተገለጹት በመንገድ እንደሚሄድ ተደርገው ነው፡፡ "እግዚአብሔር የማደርገው ምን እንደሆነ ያውቃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እንደ ወርቅ ነጥሬ እወጣለሁ

ኢዮብ መከራው እርሱ እንደ ነጠረ ወርቅ መሆኑን እንደሚያረጋግጥ ያምናል፡፡ "ማናቸውም ንጹህ ያልሆነ ነገር በእሳት ተፈትኖ ሲወገድ፣ እኔ እንደ ወርቅ ንጹህ መሆኔን ይመለከታል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

እግሮቼ የእርሱን መንገድ ጠብቀዋል

እዚህ ስፍራ "እግሬ" የሚለው የሚያመለክተው ኢዮብን ነው፡፡ "እርሱ ያሳየኝን መንገድ ተከትያለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

የእርሱን መንገድ ጠብቄያለሁ

የኢዮብ ታዛዥነት የተገለጸው እግዚአብሔር ባሳየው መንገድ እንደሄደ ተደርጎ ነው፡፡ "እርሱ አደርገው ዘንድ የነገረኝን አድርጌያለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡(ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ከዚያ ፈቀቅ አላልኩም

ይህ በአዎንታዊ መልክ ሊጻፍ ይችላል፡፡ "በትክክል ተከትያለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

ከዚያ ወደ ኋላ አልልኩም/አላፈገፈግኩም

ይህ በአዎንታዊ መልክ ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ሁልጊዜም ታዝዣለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

የእርሱ ከንፈሮች

ይህ ሀረግ የሚያመለክተው እግዚአብሔር የተናገረውን መልዕክት ነው፡፡ "እርሱ የተናገረው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

የአፉ ቃል

እዚህ ስፍራ እግዚአብሔር የተገለጸው በ "አፉ" ነው፡፡ "እርሱ የተናገረው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)