am_tn/job/23/03.md

1.7 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኢዮብ መናገሩን ቀጥሏል

አወይ፣ ያ የት እንደሆነ አውቃለሁ… አወይ፣ እኔ ወደዚያ እመጣለሁ

እነዚህ ሁለት መስመሮች ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፤ የሚያጎሉትም ኢዮብ ከእግዚአብሔር ጋር ለመገናኘት ያለውን ፍላጎት ነው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

አገኘው ይሆናል

"እግዚአብሔርን አገኘው ይሆናል"

ጉዳዬን በፊቱ አቀርብ… አፌን በሞላው

እነዚህ ሁለት መስመሮች ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፤ የሚያጎሉትም ኢዮብ ለእግዚአብሔር ሁኔታውን ለማስረዳት ያለውን ፍላጎት ነው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

አፌን በክርክር ሞላው

እዚህ ስፍራ "አፌን ሞላው" የሚለው የሚያመለክተው ንግግርን ነው፡፡ "ክርክሬን ሁሉ አቀርባለሁ/እናገራለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

ቃሎቹን እማራለሁ… እረዳቸዋለሁ

እነዚህ ሁለት መስመሮች በመሰረቱ ተመሳሳይ ትረጉም አላቸው፤ የሚያተኩሩትም ኢዮብ የእግዚአብሔርን መልስ ለመስማት ባለው ፍላጎት ላይ ነው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ለእኔ የሚሰጠኝን መልስ

"እርሱ ለእኔ የሚሰጠውን መልስ"