am_tn/job/23/01.md

1.4 KiB

ዛሬም እንኳን ሀዘኔ መራራ ነው

እዚህ ስፍራ "ዛሬም እንኳን" የሚለው የወዳጆቹ ክርክር የኢዮብን ሁኔታ ምንም እንዳለወጠው የሚያጎላ ነው፡፡ "እንንተ ከተናገራችሁት ሁሉ ባሻገር፣ የእኔ ሀዘን ዛሬም መራራ ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

ሀዘኔ መራራ ነው

ኢዮብ ስላልተመለሱ ጥያቄዎቹ በአፉ ውስጥ እንዳለ መራራ ጣዕም አድርጎ እግዚአብሔርን ተቃውሞ ይናገራል፡፡ "ያልተመለሱ ጥያቄዎቼ በአፌ ውስጥ እንደሚገኝ መራራ ምግብ ሆኖብኛል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

የእኔ እጅ ... ከማቃሰቴ የተነሳ ከብዷል

ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) "ከማቃሰቴ የተነሳ እጄን ማንሳት እንኳን አልቻልኩም" ወይመም 2) "ከማቃሰቴ ባሻገር የእግዚአብሔር እጅ እኔን ማሰቃየቱን ቀጥሏል" እዚህ ስፍራ "እጅ" የሚለው የሚያመለክተው እግዚአብሔር ለመቅጣት ያለውን ሀይል ነው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)