am_tn/job/22/26.md

1.2 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኤልፋዝ ከኢዮብ ጋር መነጋገሩን ቀጠለ

ፊትህን ወደ እግዚአብሔር ታነሳለህ

ይህ ማለት ኢዮብ ከእንግዲህ አያፍርም፣ ይልቁንም በእግዚአብሔር ይታመናል፡፡ "በሙሉ ልን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሆንልሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ይህ ለአንተ ይረጋገጥልሃል

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር ፍሬያማ ያደርግሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)

በመንገዶችህ ብርሃን ይሆናል/ይበራል

የእግዚአብሔር በረከት የተነጻጸረው በኢዮብ መንገድ ላይ ሁሉ እንደሚሆን ብርሃን ነው፡፡ "በፊትህ በሚገኝ መንገድ ላይ እንደሚበራ ብርሃን ይሆናል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)