am_tn/job/22/15.md

1.7 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኤልፋዝ ከኢዮብ ጋር መነጋገሩን ቀጠለ

ኃጢአተኞች በሚሄዱበት አሮጌ መንገድ መሄድህን ትቀጥላለህ

ክፉ ስራ መስራት የተነጻጸረው በመንገድ ላይ ከመሄድ ጋር ነው፡፡ "ክፉ ሰዎች የሚያደርጉትን ማድረግህን ትቀጥልበታለህ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እንደ ተቀሙት እንደ እነርሱ

ሞት የተነጻጸረው እግዚአብሔር እነርሱን እንደ ቀማቸው ተደርጎ ነው፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "የሞቱት እነርሱ" ወይም "እግዚአብሔር የወሰዳቸው እነርሱ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)

መሰረታቸው እንደ ወንዝ ተጠርጎ የተወሰደው

የክፉ ሰዎች ሞት የተነጻጸረው መሰረታቸው በጎርፍ ከተወሰደ ህንጻዎች ጋር ነው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ሁሉን ቻይ የሆነው በእኛ ላይ ምን ማድረስ ይችላል?

ኤልፋዝ የሚጠቅሰው ክፉዎች በእግዚአብሔር ላይ ለመሳለቅ የሚያነሱትን ጥያቄ ነው፡፡ "ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ በእኛ ላይ አንዳች ማድረግ አይችልም!" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)