am_tn/job/16/18.md

2.2 KiB

ምድር ሆይ፣ ደሜን አትሸፍኚ

ኢዮብ ሃሳቡን ለማጉላት ባትሰማውም አንኳን በቀጥታ ለ"ምድር" ይናገራል፡፡ ምድር ከሞቱ በኋላ ደሙን አውቃ እንደምትሸፍን ተደርጋ በሰውኛ ተገልጻለች፡፡ "ደሜን ምድር ሳትመጠው ከላይ ተቀምጦ እንዴት እንደሞትኩ ምስክር ቢሆን እመኛለሁ" (አፖስትሮፊ/በተለይ በአጠገብ የማይገኝን ነገር አጋኖ ለማመልከት የሚነገር ዘይቤ እና ሰውኛ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)

ምድር ሆይ፣ ደሜን አትሸፍኚ

ኢዮብ ስለ ራሱ ሞት የሚናገረው እንደሚገደል አድርጎ ነው፡፡ እዚህ ስፍራ "ደም" የሚለው የእርሱን መሞት የሚያመለክት ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ነው፡፡ "ምድር ሆይ፣ በምሞትበት ሰአት፣ አለአግባብ መሞቴን አትደብቂ" ወይም "አለ አግባብ መሞቴ አይደበቅ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

ጩኸቴ የእረፍት ስፍራ አያግኝ

ኢዮብ የእርሱ "ጩኸት" ሰው ሆኖ የደረሰበትን እና በፍጹም እረፍት ያሳጣውን ነገር ለሁሉም ሰው እንዲያሳውቅለት በመፈለግ ይናገራል፡፡ "ሁሉም ሰው በእኔ ላይ የደረሰውን ይስማ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

እነሆ

ኢዮብ ይህንን ቃል የተጠቀመው ቀጥሎ ለሚናገረው ትኩረት ለመስጠት ነው፡፡ "አድምጡኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

ይመሰክርልኛል

"ጻድቅ መሆኔን ይመሰክራል"

በላይ ያለው

ይፈሊጣዊ አነጋገር ነው፡፡ "በሰማይ" ወይም "በላይ በሰማይ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)