am_tn/job/16/15.md

2.1 KiB

በቆዳዬ ላይ ማቅ ሰፍቻለሁ

ኢዮብ ከሰውነቱ ጋር እንደ ተያያዘ ሆኖ የተሰፋ ማቅ ስለ መልበስ ይናገራል፡፡ ሰዎች ብዙጊዜ ማቅ የሚለብሱት ሀዘናቸውን ወይም ታለቅ መከራ እንደደረሰባቸው ለመግለጽ ነው፡፡ "አዝኛለሁና ማቅ ሰፍቼ እለብሳለሁ" ወይም "ከማቅ የሰፋሁትን ልብስ እለብሳለሁ፣ ምክንያቱም አዝኛለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ቀንዴን በአፈር ውስጥ እቀብራለሁ

የኢዮብ "ቀንድ" የሚወክለው ቀድሞ የነበረውን አሁን ግን ከእርሱ ጋር የሌለውን ሀይሉን እና ስልጣኑን ነው፡፡ "አሁን እዚህ በትካዜ/በጣም በድባቴ ሆኜ በትቢያ ላይ እቀመጣለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በዐይኖቼ ሽፋሽፍት የሞት ጥላ አለ

እዚህ ስፍራ የኢዮብ ዐይኖች የተወከሉት በ "ዐይኖቹ ሽፋሽፍት" ነው፡፡ ኢዮብ የዐይኖቹን መጨለም የሚገልጸው ዐይኖቹ የሞተ ሰው ዐይን እንደመሰሉ አድርጎ ነው፡፡ "በዐይኖቼ ዙሪያ ጥቁር ክቦች አሉ" ወይም "ዐይኖቼ እንደ ሞተ ሰው ዐይን ጥቁር ናቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ እና ዘይቤያዊ አነጋገር የሚሉትን ይመልከቱ)

በእጆቼ ላይ አመጽ የለም

"እጆች" የሚለው የሚወክለው የአንድን ሰው ችሎታ እና ድርጊት ነው፡፡ "በግፍ አንዳች አላደረግኩም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)