am_tn/job/16/13.md

2.2 KiB

የእርሱ ቀስተኞች ዙሪያዬን ከበውኛል

ኢዮብ ስለ ራሱ የሚናገረው የእግዚአብሔር ጥቃት ትኩረት እንደሆነ፣ እግዚአብሔር እርሱን እንደ ጥቃት ኢላማ ከፍ አድርጎ እንዳስቀመጠው የእግዚአብሔር ቀስተኞች ሊያጠቁት እንደከበቡት አድርጎ ነው፡፡ "የእርሱ ቀስተኞች ዙሪያዬን ከበውኛል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እግዚአብሔር ኩላሊቴን በስቶታል፣ ለአፍታም አልተወኝም፣ ሀሞቴን በምድር ላይ አፍስሶቶታል

ኢዮብ የደረሰበትን መከራ ስሜት የሚገልጸው እግዚአብሔር አካሉን በቀስቶች እንደበሳው በማነጻጸር ነው፡፡ እዚህ ስፍራ "እግዚአብሔር" የሚለው የሚወክለው እርሱ የሚወረውራቸውን ቀስቶች ነው፡፡ "ኩላሊቴን እና ጉበቴን የእግዚአብሔር ቀስቶች እንደወጉኝ፣ ሀሞቴ በምድር ላይ እንደፈሰሰ ይሰማኛል፡፡ እርሱ አልተወኝም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ቅጥሬን አፈረሰው

ኢዮብ የተሰማውን ስቃይ የሚገልጸው ራሱን እግዚአብሔር ካፈረሰው ግንብ ጋር በማነጻጸር ነው፡፡ "እግዚአብሔር እንዳፈረሰው ግንብ እንደሆንኩ ይሰማኛል" ወይም "እግዚአብሔር እንዳደቀቀው ግንብ እንደሆንኩ ይሰማኛል፡፡ በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እንደ ጦረኛ ወደ እኔ ይሮጣል

ኢዮብ እግዚአብሔርን የሚገልጸው እርሱን እንደሚያጠቃ ወታደር ነው፡፡ "ሊያጠቃኝ ወደ እኔ እየሮጠ እንደሚመጣ ተዋጊ ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)