am_tn/job/16/11.md

2.1 KiB

አምላክን ለማይወዱ ሰዎች አሳልፎ ሰጠኝ፣ በክፉ ሰዎች እጅ ላይ ጣለኝ

እነዚህ ሁለት መስመሮች በመሰረቱ ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፡፡ በአንድነት ሆነው የኢዮብን በእግዚአብሔር የመካድ ስሜት ያጎላሉ፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

አሳልፎ ሰጠኝ

ይህ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው፡፡ "በቁጥጥራቸው ስር አደረገኝ"

በእጃቸው ላይ ጣለኝ

እዚህ ስፍራ የሰው "እጅ" የሚያመለክተው በ"ቁጥጥሩ ስር" ማድረግን ነው፡፡ "ከተጽዕኗቸው ነጻ አውጣኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

ደግሞም እርሱ ሰባብሮኛል

ኢዮብ መከራውን እና ተስፋ መቁረጡን የሚገልጸው እርሱ ራ ወደ ትንንሽ ነገሮች እንደተሰባበረ አድርጎ ነው፡፡ "ነገር ግን የሚሰማኝ እርሱ እንደሰባበረኝ ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ቆራርጦ ጣለኝ

ኢዮብ የሚናገረው እግዚአብሔር ስቃይ እንዳደረሰበት እና ተስፋ እንዳስቆጠረው፣ እንደዚሁም ወደ ቁርጥራጭ ነገርነት እንዳደቀቀው ነው፡፡ "አንገቴን አንቆ ትንንሽ ነገር አድርጎ አድቅቆኛል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ደግሞም አላማው አድርጎ አስቀምጦኛል

ኢዮብ ራሱን የእግዚአብሔር ጥቃት ትኩረት እንደሆነና እግዚአብሔር ቀስቱን የሚያነጣጥርበት ኢላማው እንዳደረገው ይናገራል፡፡ "ኢላማው አድርጎኛል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)