am_tn/job/16/06.md

2.4 KiB

ሀዘን

ኢዮብ ያልተጠበቀና በቃላት ለመግለጽ የሚያዳግት "ታላቅ ሀዘን እና የስሜት ስቃይ" ቤተሰቡን እና ጤናውን በማጣት አጋጥሞታል

እንዴት እጸናናለሁ?

ኢዮብ ይህንን ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የተጠቀመው ዝም ማለቱ ስቃዩን ለማቃለል እንዳልረዳው ለመግለጽ ነው፡፡ ይህ ጥያቄ በገለጻ/ዐረፍተ ነገር መልክ ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ይህ ምንም አልረዳኝም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ነገር ግን አሁን፣ እግዚአብሔር ሆይ፣ አንተ

ኢዮብ አሁን ማጉረምረሙን ወደ እግዚአብሔር ዞር ያደርገዋል

ቤተሰቤን ሁሉ አጠፋህ

"ቤተሰቤን ሁሉ ደመሰስህ"

አንተ እኔን አደረቅኸኝ

ይህ ማለት የኢዮብ አካል ከሳ ቆዳው ተሸበሸበ ማለት ነው፡፡ "ከሰውነት ተራ ወጣሁ አካሌን አከሳኸው" (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)

ይህ ራሱ ይመሰክርብኛል

ኢዮብ የሰውነቱን መክሳት በእርሱ ላይ ከሳሽ እንደሆነ አድርጎ ያቀርበዋል፡፡ "ደግሞም ይህ ሰዎች እኔን ኃጢአተኛ አድርገው እንዲያስቡ ያደርጋቸዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

የሰውነቴ ክሳት በእኔ ላይ ተቃዋሚ ሆኖ ይነሳብኛል፣ ምስክርም ይሆንብኛል

ኢዮብ የአካሉን መክሳት በእርሱ ላይ ከሳሽ እንደሆነበት ይገልጻል፡፡ "ምን ያህል እንደከሳሁ ይመለከታሉ፣ ይህም ደግሞ እኔ ኃጢአተኛ እንደሆንኩ ያረጋግጣል ብለው ያስባሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ፊቴ ላይ

እዚህ ስፍራ ኢዮብ የተጠቀሰው በእርሱ "ፊቱ" ነው፡፡ "በእኔ ላይ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)