am_tn/job/14/20.md

1.6 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገሩን ይቀጥላል፡፡

አንተ ሁልጊዜም እርሱን ታሸንፋለህ

"እርሱ" የሚለው ቃል ማናቸውንም ሰው ያመልክታል፡፡ "አንተ ሁልጊዜም ሰውን ታሸንፋለህ" ወይም "አንተ ሁልጊዜም ሰዎችን ታሸንፋለህ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

እርሱ ያልፋል

ማለፍ የሚለው የሚወከወለው/የሚገልጸው ሞትን ነው፡፡ "እርሱ ይሞታል" (ዩፊምዝም/ የማያስደስትን ቃል ሻል ባለ ቃል መተካት የሚለውን ይመልከቱ)

አንተ ፊቱን ትለውጣለህ

ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) ከመሞቱ አስቀድሞ የሚገጥመው ስቃይ ፊቱ እንዲጨማደድ ያደርጋል ወይም 2) አንድ ሰው ሲሞት፣ እግዚአብሔር የሰውየውን ፊት የተለየ ያደርገዋል

እንዲሞት ይተወዋል/በሞት ይሸኘዋል

ይህ የሚገልጸው እንዲሞት ማድረግን/መፍቀድን ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ዝቅ ከተደረጉ/ከተዋረዱ

መዋረድ/ዝቅ መደረግ የሚለው የሚገልጸው ወይም የሚወክለው እንዲያፍር መደረግን ነው፡፡ "እንዲዋረዱ ከተደረገ" ወይም "ሰዎች ካሳፈሯቸው/ካዋረዷቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)