am_tn/job/14/15.md

3.7 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገሩን ይቀጥላል፡፡

እኔ መልስ እሰጣለሁ

"እኔ ምላሽ እሰጣለሁ"

ትፈልገኛለህ/ትናፍቃለህ

"ፍላጎት" የሚለው ስም "ፈለገ" ወይም "ወደደ" በሚል ግስ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "አንተ ትፈልጋለህ/ትናፍቃለህ" ወይም "አንተ ትወዳለህ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

የእጆችህ ስራ

እዚህ ስፍራ የእግዚአብሔር እጆች የሚወክሉት እርሱ ነገሮችን መስራቱን ነው፡፡ ኢዮብ ራሱን የእግዘአብሔር የእጆቹ ስራ አድርጎ ይገልጻል፡፡ "አኔን ያበጀኸኝ አንተ ነህ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት እና አንደኛ፣ ሁለተኛ እና ሶስተኛ መደብ የሚሉትን ይመልከቱ)

ቁጥር እና መቆጣጠር/መከታተል

እነዚህ ሁለት ግሶች ሁለቱ በአንድነት አንድን ድርጊት ይገልጻሉ፡፡ "በንቃት ትከታተላለህ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሄንዲየዲስ/ሁለት ቃላት ‘እና' በሚል አያያዥ ቃል የሚገኛኙበትና አንድን ጥልቅ ሀሳብ ለመግለጽ የሚያገለግል ዘይቤያዊ አነጋገር)

የእግሬ ኮቴ/እርምጃዬ

እርምጃ/ኮቴ የሚለው የሚወክለው ህይወቱን ወይም ያደረገውን ነው፡፡ "ህይወቴ" ወይም "ያደረግኳቸው ነገሮች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

አትቆጥርብኝም… መተላለፌን ይቅር ትላለህ…አንተ ትሸፍንልኛለህ

እነዚህ ሶስት ሀረጎች ተመሳሳይ ሀሳብን ይገልጻሉ፣ በአንድነት የዋሉት እግዚአብሔር ይቅር እንደሚለው ያለውን እርግጠኝነት/ልበሙሉነት ለመግለጽ ነው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ኃጢአቴን አትቆጥርብኝም

የኢዮብን ኃጢአት አለመቁጠር የሚወክለው ስለ እርሱ ኃጢአት አለማሰብን ነው፡፡ "ኃጢያቴን አትመለከትም" ወይም "ስለ እኔ ኃጢአት አታስብም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

መተላለፌን በከረጢት ውስጥ ታትምበታለህ

መተላለፍን በከረጢት ማተም የሚለው የሚገልጸው ኃጢአትን መሸፈን እና ስለ እርሱ ማሰብን አለመፍቀድ ነው፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "አንድን ነገር በከረጢት ውስጥ እንደደበቀ ሰው መተላለፌን ማሰብ አትፈቅድም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በደሌን ትሸፍናለህ/ይቅር ታላለህ

እንዳይታይ የአንድን ሰው በደል መሸፈን የሚወክለው ስለዚያ ማሰብን አለመፍቀድን ነው፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "በደሌን ትሸፍናለህ" ወይም "ኃጢአቴን ትተውልኛለህ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)