am_tn/job/14/13.md

2.1 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገሩን ይቀጥላል፡፡

አቤቱ፣ እባክህ ሰውረኝ

ይህ ኢዮብ በጣም የሚፈልገውን ነገር ግን በእርግጥ ይሆናል ብሎ የማይጠብቀውን ነገር የሚያሳይ ቃለ አጋኖ ነው፡፡ "ብትሰውረኝ በወደድሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ አጋኖ የሚለውን ይመልከቱ)

ለብቻዬ አግልለኝ

"በእኔ ላይ ቆልፍ" ወይም "ሰውረህ አስቀምጠኝ"

አትርሳኝ

አንድን ሰው አለመርሳት/ማስታወስ ስለዚያ ሰው ማሰብን የሚገልጽ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው፡፡ "ስለ እኔ አስብ" ወይም "እኔን አስታውስ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

የሞተ ሰው ዳግም ይኖራልን?

በውስጠ ታዋቂነት የተሰጠ ምላሽ "አይ" የሚል ነው፡፡ "የሞተ ሰው፣ ዳግም በህይወት አይኖርም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

እንዲህ ከሆነ

"ከሆነ" የሚለው ምን እንደሚያመለክት ከቀደመው ሀረግ ይታወቃል፡፡ "እርሱ ዳግም ቢኖር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)

የድካም ጊዜያቶቼን ሁሉ በዚያ ለመቆየት

"ብደክም እንኳን ዘመኔን ሁሉ በዚያ ለመቆየት"

የመለቀቅ/የመታደስ ጊዜዬ እስኪደርስ

"መለቀቅ/መታደስ" የሚለው ረቂቅ ስም "ተለቀቀ/ታደሰ" በሚል ግስ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እስከምለቀቅ ድረስ" ወይም "አንተ እስከምትለቀኝ/እስክታድሰኝ ድረስ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)