am_tn/job/14/04.md

2.1 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገሩን ይቀጥላል፡፡

ማን ንጹህ ካልሆነ ነገር ንጹህ የሆነ ነገርን ማውጣት ይችላል? ማንም

ኢዮብ ይህንን ጥያቄ የሚጠቀመው እርሱ ንጹህ ስላልሆነ ነገር የሚያውቀውን እግዚአብሔር በኢዮብ ላይ እንዲያደርግ ለመገፋፋት ነው፡፡ "ማንም ንጹህ ካልሆነ ነገር ንጹህ ነገርን ማምጣት አይችልም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

የሰው ቀኖች የተወሰኑ ናቸው

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "አንተ የሰውን ቀናት ትወስናለህ" ወይም "አንተ ሰው የሚኖርበትን ዘመን ትወስናለህ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)

የወራቱ ቁጥር በአንተ ዘንድ ነው

ሰው የሚኖርበት ወራት ቁጥር በእግዚአብሔር ዘንድ መሆኑ የሚወክለው ሰው የሚኖርበትን ወራት ቁጥር የሚወስነው እግዚአብሔር መሆኑን ነው፡፡ "ምን ያህል ወራት እንደሚኖር አንተ ትወስናለህ" (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

ሊያልፍ የማይችልበትን ገደብ አንተ ወስነሀል

ገደብን ማለፍ የሚለው የሚወክለው አንድ ሰው እንዲኖር እግዚአብሔር አስቀድሞ የወሰነለት ዘመን መኖር ነው፡፡ "አንተ የሚሞትበትን ጊዜ ወስነሃል፣ እናም ሰው ያንን አልፎ መኖር አይችልም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

የተቀጠረ ሰው/ቅጥረኛ

አንድን ስራ ለመስራት የተቀጠረ እና ከዚያ ወደ ቤቱ የሚሄድ ሰው