am_tn/job/13/16.md

1.7 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኢዮብ ለወዳጆቹ መናገሩን ጨርሶ በቀጥታ ከእግዚአብሔር ጋር መናገር ይጀምራል፡፡

ይህ ለእኔ ነጻ መውጣት ምክንያት ይሆናል

"ነጻ መውጣት" የሚለው ረቂቅ ስም "ነጻነት" በሚለው ግስ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር እኔን ነጻ የሚያወጣበት ምክንያት ይህ ነው" ወይም "እግዚአብሔር እኔን ከችግሮቼ የሚያድነኝ ከዚህ የተነሳ ነው" በሚሉት ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

እግዚአብሔር ሆይ፣ ስማኝ

ኢዮብ ንግግሩን የሚጀምረው በቀጥታ ወደ እግዚአብሔር በመጮህ/በመናገር ነው፡፡

ንግግሬን እድምጥ፣ የምናገረው ወደ ጆሮህ ይድረስ

እነዚህ ሁለት መስመሮች በመሰራታዊነት ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፤ ደግሞም ኢዮብ እግዚአብሔር እንዲሰማው የሚያቀርበውን ጥያቄ አጉልተው ይገልጻሉ፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

የምናገረው ወደ ጆሯችሁ ይድረስ

"መናገር/ማወድ" የሚለው ረቂቅ ስም "ተናገረ/አወጀ" በሚል ግስ ሊገለጽ ይችላል፡፡ ጆሯችሁ የሚለው የሚወክለው መስማትን ነው፡፡ "የምናገረውን ስሙ" ወይም "የምለውን ስሙ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች እና ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚሉትን ይመልከቱ)