am_tn/job/13/13.md

2.1 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ኢዮብ ለወዳጆቹ መናገሩን ይቀጥላል

የእናንተ ሰላም ለእናንተ ይሁን/ሰላማችሁን ያዙት

ይህ ፈሊጣው አገላለጽ ነው "ዝም በሉ" ወይም "መናገራችሁን አቁሙ" ማለት ነው፡፡(ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እኔን ብቻዬን ተዉኝ

ይህ ፈሊጣው አገላለጽ ነው "እኔኝ መሳሰጨነቃችሁን አቁሙ" ወይም "እኔን ማስተጓጎላችሁን አቁም" ነው፡፡(ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በእኔ ላይ የሚደርሰው ይድረስብኝ/ይምጣብኝ

በአንድ ሰው ላይ የሚመጡ ነገሮች የሚወክሉት በዚያ ሰው ላይ የሚሆኑ ነገሮችን ነው፡፡ ይህ አገላለጽ የሚጀምርበት "ይሁን" የሚለው አባባል በእርሱ ላይ ስለሚደርሰው ነገር ግድ የለውም ማለት ነው፡፡ "በእኔ ላይ ሊደርስ ያለው ማናቸውም ነገር ይድረስብኝ" ወይም "በእኔ ላይ ስለሚደርሰወ ነገር ግድ አይለኝም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ስጋዬን … በእጆቼ አይዛለሁ

እዚህ ስፍራ "ስጋ" የሚለው ለህይወት ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ነው፡፡ "ጥርስ" እና "እጆች" የሚሉት ራሱን ስለ መግዛቱ ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁለት ሀረጋት በአንድነት ኢዮብ ከእግዚአብሔር ጋር በመከራከር ህይወቱን አሳልፎ ለመስጠት ፈቃደኛ መሆኑን ያጎላሉ፡፡ "ህይወቴን አሳልፌ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ" (ሜቶኖሚ/ ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)