am_tn/job/12/13.md

2.6 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ12፡13 እግዚአብሔር ጠቢብ እና ታላቅ ነው ይላል፡፡ የምዕራፉ ቀሪ ክፍል እግዚአብሔር ስለ ሰራቸው በጥበብ የተሞሉ እና ታላላቅ ስራዎች በመናገር ይህ እውነት መሆኑን ያሳያል፡፡

ጥበብ እና ታላቅነት የእግዚአብሔር ናቸው

"ጥበብ" እና "ታላቅነት" የሚሉት ረቂቅ ስሞች "ጠቢብ" እና "ታላቅ" በሚሉ ቅጽሎች ሊገለጹ ይችላሉ፡፡ "እግዚአብሔር ጠቢብ እና ታላቅ ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

እነሆ/ተመልከት

"እይ" ወይም "አድምጥ" ወይም "ልነግርህ ስላለው ነገር ትኩረት ስጥ"

ይህ ዳግም ሊገነባ አይችልም

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ይህን ማንም ዳግም ሊገነባው አይችልም" (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)

እርሱ ያሰረውን፣ ሊፈታው የሚችል የለም

"መፍታት" የሚለው ረቂቅ ስም "ነጻ" በሚለው ግስ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር ያሰረውን፣ ማንም ነጻ ሊያወጣው አይችልም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

እርሱ ውሆችን ከገደበ፣ ይደርቃሉ

ውሃን መገደብ/መያዝ የሚለው ሊኖረው የሚችለው ትርጉሞች 1) ዝናብ እንዳይዘንብ ቢከለክል፡፡ "ዝናብ እንዳይዘንብ ቢከለክል ምድር ትደርቃለች" ወይም 2) ወራጅ ውሃን ከመፍሰስ ቢያስቆም፡፡ "ውሃ እንዳይወርድ ቢያግድ ምድር ትደርቃለች" በሚሉት ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እርሱ ቢለቃቸው፣ ምድሩን ያጥለቀልቃሉ

ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች፤ እነርሱን መልቀቅ የሚለው ዘይቤ ነው ትርጉሙም 1) ዝናብ እንዲዘንብ ቢያደርግ/ዝናብን ቢያዘንብ፡፡ "ብዙ ዝናብ ቢያዘንብ፣ ምድሪቱ ትጥለቀለቃለች" ወይም 2) ውሃ እንዲወርድ/እንዲፈስ ቢያደርግ፡፡ "ብዙ ውሃ እንዲወርድ ቢያደርግ፣ ምድር ትጥለቀለቃለች" በሚሉት ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)