am_tn/job/12/07.md

2.7 KiB

ነገር ግን አሁን ጠይቁ…ለእናንተ ያሳውቋችኋል

እነዚህ 4 ሃሳቦች፤ አውሬዎች፣ ወፎች፣ ምድር እና አሶች ሁሉም ከኢዮብ ወዳጎች ይልቅ እግዚአብሔርን መረዳት እንደሚችሉ ይገልጻሉ፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ እና ምፀት የሚሉትን ይመልከቱ)

እናንተ

ይህ በኢዮብ ቁጥር 7 እና 8 ላይ ብዙ ቁጥር ነው፡፡ (አንተ የሚለውን ተውላጠ ስም መልኮች ይመልከቱ)

ነገር ግን አሁን አውሬዎችን ጠይቁ እነርሱም ያስተምሯችኋል

በዐረፍተ ነገሩ የመጀመሪያ ክፍል ላይ የሚገኘው ትዕዛዝ እንደ መላምታዊ ሁኔታ ሆኖ ያገለግላል፡፡ "አውሬዎችን ብትጠይቁ ኖሮ፣ እነርሱ ባስተማሩዋችሁ ነበር፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስልጣን እና ሃላፊነቶች - ሌሎች ጥቅሞች እንዲሁም መላምታዊ ሁኔታዎች የሚሉትን ይመልከቱ)

የሰማይ ወፎችን ጠይቁ፣ እነርሱም ይነግሯችኋል

በዐረፍተ ነገሩ የመጀመሪያ ክፍል ላይ የሚገኘው ትዕዛዝ እንደ መላምታዊ ሁኔታ ሆኖ ያገለግላል፡፡ የሰማይ ወፎችን ብትጠይቁ ኖሮ፣ እነርሱ ባስተማሩዋችሁ ነበር፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስልጣን እና ሃላፊነቶች - ሌሎች ጥቅሞች እንዲሁም መላምታዊ ሁኔታዎች የሚሉትን ይመልከቱ)

ወይም ከምድር ጋር ተነጋገሩ፣ እርሷ ታስተምራችኋለች

በዐረፍተ ነገሩ የመጀመሪያ ክፍል ላይ የሚገኘው ትዕዛዝ እንደ መላምታዊ ሁኔታ ሆኖ ያገለግላል፡፡ "ወይም ከምድር ጋር ብትነጋገሩ ኖሮ፣ ባስተማረቻችሁ ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስልጣን እና ሃላፊነቶች - ሌሎች ጥቅሞች እንዲሁም መላምታዊ ሁኔታዎች የሚሉትን ይመልከቱ)

የባህር አሶች ያሳውቋችኋል

"የባህር አሶችን ጠይቁ" የሚለው ትዕዛዝ ከቀደሙት ዐረፍተ ነገሮች ለማለት የተፈለገው ይታወቃል፡፡ እንደ መላምታዊ ሁኔታ ሆኖ ይሰራል፡፡ "የባህር አሶችን ብትጠይቁ ኖሮ፣ ለእናንተ ያሳውቋችሁ ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (የተዘለለ/የተተወ እና ስልጣንና ሃላፊነቶች - ሌሎች ጥቅሞች እንዲሁም መላምታዊ ሁኔታዎች የሚሉትን ይመልከቱ)